ተሐድሶአዊ
በሕይወት ሁሉ ላይ የእግዚአብሔርን ሉዓላዊነት እናምናለን።
ተጨማሪ ያንብቡእግዚአብሔርን ለማምለክ፣ ቃሉን ለማጥናትና እምነታችንን በአንድነት ለመኖር ወደምንሰበሰብበት ወደ GRBC እንዲቀላቀሉን እንጋብዝዎታለን። ለተሐድሶ እምነት አዲስ ቢሆኑም ሆነ ከእግዚአብሔር ጋር ያለዎትን ኅብረት የሚያሳድጉበትን ስፍራ የሚፈልጉ ቢሆኑ፣ በመካከላችን እንኳን ደህና መጡ።
ያግኙን
የቅዱሳት መጻሕፍትን ሥልጣን እናምናለን፤ በታማኝነት ልናስተምረውና ሕይወታችንን በእግዚአብሔር ቃል ልንመራ እንተጋለን።
አምልኳችን መሥዋዕቱንና ሉዓላዊነቱን በመቀበል በኢየሱስ ክርስቶስ ማንነትና ሥራ ላይ ያተኮረ ነው።
በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ስብከትና በጸሎት ላይ በሚያተኩሩ ተሐድሶአዊ የአምልኮ አገልግሎቶች ይቀላቀሉን።
እንደ 1689 የለንደን አጥማቂያን የሃይማኖት መግለጫ ያሉ ታሪካዊ ተሐድሶአዊ መግለጫዎችን እንይዛለን፤ የእግዚአብሔርን ሉዓላዊነት፣ የጸጋ ትምህርቶችንና በሁሉ ነገር የክርስቶስን ማዕከልነት እናጎላለን።
ተሐድሶአዊ አጥማቂ ቤተ ክርስቲያን እንደመሆናችን፣ የአማኞችን ጥምቀት በመስመጥ እንፈጽማለን፤ ይህም ለክርስቶስ ትእዛዝ በደስታ መታዘዝና በእርሱ ያለንን እምነት በይፋ መግለጽ ነው።
ከብሉይ ኪዳን እስከ አዲስ ኪዳን በቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ ያለውን የእግዚአብሔር የቤዛነት ዕቅድ አንድነት በመቀበል የቃል ኪዳን ሥነ መለኮትን እናስተምራለን።
ከመጋቢያችንና ከሽማግሌዎቻችን በሰንበትና በሌሎች ስብሰባዎች የተሰበኩ በርካታ ስብከቶች፣ እንዲሁም ከታላላቅ ተሐድሶአዊ የመዝሙር ደራስያን የተተረጎሙ መዝሙሮች አሉን።
አብዛኞቻችን ካደግንበት ሁኔታ አንጻር አንዳንድ ልምምዶች በቀላሉ አይለቁንም። ያደግንበት አካባቢ በቀጥታ “Charismatic” ባይሆንም እንኳ፣ አዕምሮአችን የተቀረጸውና የተገነባው በዚያው አስተሳሰብ ሊሆን ይችላል። ይህ ሁኔታ በብዙ…
ተጨማሪ ያንብቡ